Saturday, 18 May 2013
You are here: Home
የኢትዮጵያ ፖሰታ አገልግሎት ድርጅት ሁለት የጭነት መኪኖች ግዥ አከናወነ PDF Print E-mail

የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ከ35 እስከ 45 ኩንታል የመጫን አቅም ያላቸው ሁለት የጭነት መኪኖችን (cargo trucks) ግዥ አከናወነ፡፡ የተሽከርካሪዎቹ ሙሉ ወጪ በድርጅቱ የተሸፈነ ሲሆን መኪኖቹን ለመግዛት በአጠቃላይ 897,000.00 /ስምንት መቶ ዘጠና ሰባት ሺህ ብር/ ወጪ ተደርጓል፡፡

ተሽከርካሪዎቹ አገልግሎት መስጠት ሲጀምሩ ድርጅቱ ያለበትን የተሽከርካሪ እጥረት ከማቃለሉም ባሻገር ድርጅቱ ለአገለገሉ መኪኖች የሚያ ወጣውን ወጪ ከመቀነስ አኳያ ሁነኛ ሚና እንደሚኖራቸው ለመረዳት ተችሏል፡፡